ጸጋ የመጽሐፍ ቅዱስ ኅብረት ቤተ ክርስቲያን

ስለ ጌታችንና መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ከአማርኛ ተናጋሪ ቤተ ክርስቲያን አባላት ጋር ለመማር፣ ለማምለክ እና ለማክበር የጸጋ የመጽሐፍ ቅዱስ ኅብረት ቤተክርስቲያንን ይቀላቀሉ።

እንኳን ደህና መጡ!

የቤተክርስቲያን አገልግሎት

እግዚአብሔርን በማምለክ፣ በመጸለይ እና ስለ ኢየሱስ ክርስቶስ ያለንን ግንዛቤ በምናሳድግበት አንድ ላይ በምንሰባሰብበት ትርጉም ያለው ፕሮግራም ላይ ይቀላቀሉን።

Sunday
Schedule
3:30pm EST
Time
65 Sunrise Ave
Address

በአካል የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናት እና ጸሎት

በአካል በመገናኘት በምናደርገው የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናት ላይ ይቀላቀሉን። በዚህ ጊዜ ኢየሱስን የምናከብርበት፣ እራሳችንን የምናንጽበት እና መንፈሳዊ ማንነታችንን የምናዳብርበት በአካል ለምናደርገው የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናት እና ጸሎታችን ይቀላቀሉን።

Friday
Schedule
7:30pm EST
Time
100 Halsey Ave
Address

ኦንላይን የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናት

ኦንላይን በመገናኘት በምናደርገው የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናት ላይ ይቀላቀሉን። የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናት ክፍለ ጊዜዎች ከቤትዎ ሆነው መንፈሳዊ ጉዞ ይጀምሩ። በስልክ ቁጥር 416-839-7968 ወይም 647-608-8189 ዕሮብ 7፡30 PM

Weekly
Schedule
7:30pm EST
Time
Online
Address

እንዴት እንደምናገለግል

የእሁድ አገልግሎት

የቤተ ክርስቲያናችንን አባሎች በመጽሐፍ ቅዱሳዊ ትምህርት ደቀመዛሙርት ማድረግና ጥሪያቸውን በሚገባ አውቀው አምላካቸውን እንዲያገለግሉ ማስታጠቅ እና በጸሎት፣ በአምልኮ እና የእግዚአብሔርን ትእዛዝ እንዲታዘዙ የአባሎቻችንን እምነት እናሳድጋለን።

የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናት

የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናት ለክርስቲያኖች በጣም አስፈላጊ ነው ምክንያቱም አማኞች እምነታቸውን እንዲያድግ ፤ ከአምላካቸው ጋር ያላቸውን ዝምድና እንዲጠነክርና የጽድቅን ሕይወት እንዲመሩ እናስጠናቸዋለን።

ጸሎት

በየሳምንቱ በእምነት እና በአንድነት መንፈስ በአምላካችን እግር ሥር ልባችንን ለማፍሰስ እንሰበሰባለን። በዚህ ጊዜ ስለ ልጆችና ወጣቶች ፤ ስለ ሀገር ፤ ስለ ትሁት ልብ ፤ ስለ ጽኑ እምነት ፤ ስለ ፈውስ ፤ ስለ ሰላም ፤ ስለ ፍቅር ፤ ስለ ደስታ ፤ እና ስለ መንፈስ ፍሬዎች . . ወዘተ እንፀልያለን።

ወጣት አዋቂዎች

ጎልማሶችን በፍቅር እና በጥበብ በመምራት በኢየሱስ ክርስቶስ በእምነት ወደተሞላ ሕይወትና ልባቸውን በኢየሱስ ክርስቶስ መንገድ ላይ እንዲያደርጉ በመንከባከብ መንገዱን እንዲያውቁ እናግዛቸዋለን።

ልጆች

ልጆችን በፍቅር እና በጥንቃቄ በመምራት የኢየሱስ ክርስቶስን ትምህርት እናስተዋውቃቸዋለን። ከእድሜ ጋር በሚስማማ ትምህርት እና ጸሎት እምነታቸውን ለማሳደግ እንጥራለን።

ጥምቀት

አንድ አማኝ በኢየሱስ ክርስቶስ ላይ ያለውን እምነት በውሃ ውስጥ በመጥለቅ፣ በኃጢአት ንስሐ እና እርሱን ለመከተል ቃል መግባታቸውን የሚያሳዩበት ትርጉም ያለው መንፈሳዊ ሥርዓት በመሆኑ ከመሠረታዊ የክርስትና ትምህርት በመቀጠል እናጠምቃለን።

የጥናት ቡድኖች

ትርጉም ላለው ህብረት፣ መንፈሳዊ እድገት እና በእምነት ጉዞዎ ውስጥ ድጋፍ ለማግኘት የቅርብ የተሳሰረ የጥናት ቡድኖቻችንን ይቀላቀሉ።

ይምጡ እና የለውጥ ተሞክሮ አካል ይሁኑ።

ይህ ተሞክሮ የተቻለው ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ባመጣው ድህንነ ነው።